ግራሚ አዋርድ ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳን አስታውሷል።
Grammy Award እ.አ.አ 2020-2021 የዓለም የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ካጣቸው አርቲስቶች እና የሙዚቃ ሰዎች ዝርዝር ዉስጥ የሀገራችንን ድምፃዊ አርቲስት ሃጫሉን ሀንዴሳን አካቷል።
አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ያለፈው ዓመት ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓ/ም ምሽት አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በጥይት ተመትቶ መገደሉ አይዘነጋም።
አርቲስት ሃጫሉን ሚሊዮኖች እንደ ድምፃዊ ብቻ ሳይሆን እንደነፃነት ታጋይ ፣ እንደጭቁን ህዝቦች ድምፅ፣ እንደሰብዓዊ መብት ተሟጋችም ጭምር ነው የሚያዩት።
በህይወት እያለ ለህዝብ ያቀረባቸው ሙዚቃዎቹ በሀገሪቱ ውስጥ ሲደረግ ለነበረው የፖለቲካ ፣ የነፃነት ትግል እና ጥያቄ ሚሊዮኖችን ለለውጥ እንዳነሳሳ ይታመናል።