amanuel shared a post  
1 year ago

1 year ago

#monkeypox(Ethiopia)

በኢትዮጵያ ፤ በዝንጀሮ ፈንጣጣ ሳይያዙ አልቀሩም ተብሎ #የተጠረጠሩ 2 ሰዎች ለይቶ ማቆያ እንዲገቡ መደረጋቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ምንም በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር / ኬዝ ካለበራቸው አሁን ላይ የተጠረጠሩ ኬዞችን ለዓለም ጤና ድርጅት ሪፖርት ካደረጉ 7 ሀገራት አንዷ ናት ተብሏል (ሀገራቱ ኢትዮጵያ፣ ጊኒ፣ ላይቤሪያ፣ ሞዛምቢክ ፣ ሴራሊዮን ፣ ሱዳን፣ ዩጋንዳ ናቸው) ።

ሁለቱ ተጠርጣሪዎች ናሙናቸው ውጭ ሀገር ተልኮ የምርመራ ውጤቱ እስኪታወቅ በለይቶ ማቆያ ይቆያሉ የተባለ ሲሆን ገለሰቦቹ ከፍተኛ የቆዳ በሽታ ምልክት ይታይባቸዋል ነው የተባለው።

አንድ ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ የጤና ሚኒስቴር ባለስልጣን ከሁለቱ አንደኛው ግለሰብ አሁን ላይ ከዝንጀሮ ፈጣጣ ውጪ የሌላ ምልክት እያሳየ ነው ብለዋል።

ሀገራችን ኢትዮጵያ የዝንጀሮ ፈንጣጣ መመርመሪያ የሌላት ሲሆን የተጠርጣሪዎቹ ናሙና መቼ ወደውጭ ሀገር እንደተላከ እንዲሁም ውጤቱ መቼ እንደሚደርስ የታወቀ ነገር እንደሌለ ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

image