ቂምን ሻረውና ወይ ፍቅርን አንግሰው
ሁለት ሆኖ አያውቅም አንድ ነው አንድ ሰው Teddy Afro new music - ቴዲ አፍሮ አዲስ ዘፈን
https://youtu.be/1hMVeENjVew
ቂምን ሻረውና ወይ ፍቅርን አንግሰው
ሁለት ሆኖ አያውቅም አንድ ነው አንድ ሰው Teddy Afro new music - ቴዲ አፍሮ አዲስ ዘፈን
https://youtu.be/1hMVeENjVew
በአዲስ አበባ የኤልክትሪክ አውቶቡስን ስራ ላይ ለማዋል ፋይናንስ የማፈላለግ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ቢሮ አሳውቋል።
ቢሮው በውጭና ሀገር ውስጥ ከሚገኙ የሚመለከታቸው አካላት ለአውቶቡስ ግዥ የሚውል ፋይናንስ የማፈላለግ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።
የኤልክትሪክ አውቶቡሶች ሌሊት ቻርጅ አድርገው ቀኑን በሙሉ ያለምንም የጊዜ ብክነት አገልግሎት እንዲሰጡ ይደረጋሉ ያለው ቢሮው።
አውቶቡሶቹ የሙከራ ትግበራ የሚደረግባቸው በሸገር እና አንበሳ አውቶቡሶች ሲሆን ፥ ከሸጎሌ ዴፖ ቅርበት ያላቸው አራት ኮሪደሮች ልየታ መከናወኑም ተገልጿል።
የመጀመሪያው ኮሪደር ከአዲሱ ገበያ - ቄራ ሲሆን፥ ሁለተኛው ኮሪደር መነሻውን ዊንጌት አድርጎ መዳረሻው አየር ጤና ይሆናል።
እንዲሁም ሶስተኛው ኮሪደር ከለገሃር ተነስቶ መዳረሻው ድል በር እንዲሁም አራተኛው ኮሪደር ከአውቶቡስ ተራ - አስኮ ይሆናል፡፡
ከዴፖው ያላቸው ርቀት፣ ከBRT ኮሪደሮች ጋር ያላቸው ትስስር እና ገበያ አካባቢዎች መሆናቸው ለኮሪደሮች የሙከራ ትግበራ መመረጥ እንደመስፈርት ተቀምጧል፡፡
በቀጣይ በከተማዋ ሌሎች ተጨማሪ ኮሪደሮችን በማጥናት የተደራሽነት አድማሱን የማስፋት ስራ እንደሚሰራ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ገልጿል።