A Ma Maniére x Air Jordan 2 "Airness" DO7216-100 AMM Joint AJ2 Outflow Early!
https://www.newjordans.co.uk/2....022-new-a-ma-maniere


A Ma Maniére x Air Jordan 2 "Airness" DO7216-100 AMM Joint AJ2 Outflow Early!
https://www.newjordans.co.uk/2....022-new-a-ma-maniere
የጠቅላይ ሚኒስትሩ መግለጫ
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተናጠል ተኩስ አቁሙ #የመጨረሻው ሰላማዊ ዕድል ነው አሉ።
ጠ/ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት ዛሬ ለህዝብ ባሰራጩት አጭር መግለጫ ነው።
በመግለጫቸው ላይ ፥ "ለትግራይ ሕዝብ ያለንን ሐሳብ ፤ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ያለንን ቦታ ለመጨረሻ ጊዜ አሳይተናል" ያሉት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ "ግጭት ላለማባባስ፣ ለሕዝቡ የእርሻ ወቅት ፋታ ለመስጠት እንዲሁም የርዳታ አቅርቦቱ ያለ ሰበብ እንዲከናወን ስንል በሰብአዊነት ላይ የተመሠረተ የተናጠል የተኩስ አቁም አድርገናል" ሲሉ ገልጸዋል።
አክለውም ፤ "ሰላም የተወሰነ ዋጋ እንደሚያስከፍለን ብናውቅም ይህ ግን የመጨረሻ ሰላማዊ ዕድል ነው" ሲሉ አሳውቀዋል።
እሳቸው "ጁንታ" እያሉ የሚጠሩት የህወሓት ቡድን "የሰላም መንገድ ሊዋጥለት አልቻለም ፤ አሁን ባለው ቁመናው ያለ ግጭት ውሎ ማደር አይችልም፤ ሕጻናትና ወጣቶችን በአደንዛዥ ዕጽ እያሳበደ ወደ ጦርነት እየማገደ ይገኛል" ብለዋል።
የመከላከያ ሠራዊቱ እነዚህን ሕጻናት ወታደሮች የመታደግ ሞራላዊ ግዴታ ወድቆበታል ሲሉም ገልጸዋል።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ፤ "ለሕዝባችን ስንል የከፈልነው ዋጋ ባልገባቸው ደካሞች ምክንያት ውጤት አላመጣም" ያሉ ሲሆን "ጁንታ" ሲሉ የሚጠሩት ህወሓት የኢትዮጵያ ህልውና ቀንደኛ ጠላት መሆኑን ደግሞ እያስመሰከረ ነው ብለዋል።
ይሄን መላ ሕዝቡን በማስተባበር እንቀለብሰዋለን ሲሉም ገልፀዋል።
ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ ፥ "በአንድ በኩል ሰብአዊ ርዳታ እንዲቀላጠፍ እየሠራን በሌላ በኩል የውጭና የውስጥ ጠላቶች ተናበው የከፈቱብንን ጥቃት መክተን እንቀለብሰዋለን" ሲሉ በመግለጫቸው ላይ አስፍረዋል።