ExpressAfrica
    • Advanced Search
    • People
    • African Wiki 
    • Market
    • Add Product
    • Jobs
    • COVID-19 Update 
  • Join
    • Login
    • Signup
News Cover Image
User Image
Drag to reposition cover
News Profile Picture
News
  • My Wall
  • Groups
  • Following
  • Followers
  • Likes
  • Photos
  • Videos
News profile picture
News
3 days ago

#ተጨማሪ

" የስራ ሰዓት ከጠዋቱ 12 ሰአት እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ብቻ ነው " - የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ

ተቋርጦ የነበረው የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ከነገ ጀምሮ ባጃጆቹ በተመደቡላቸው መስመሮች ብቻ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።

በመግለጫው ምን ተባለ ?

- ከአገልግሎቱ ጋር በተያያዘ ለተፈጠሩ ችግሮች መንስኤ ናቸው የተባሉት ፦
• ህግን አክብሮ አገልግሎት አለመስጠት፣
• በአብዛኛው አሽከርካሪ ዘንድ ደረጃውን የሚመጥን መንጃ ፍቃድ አለመያዝ
• የታሪፍ ስርዓት አለመኖር ዋንኞቹ ናቸው።

- አሁን በተዘጋጀ መመሪያ መሰረት ቢሮው በለያቸው የስምሪት መስመሮች አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል።

- 138 ጊዜአዊ ታፔላዎችን ከዋናው መስመር ውጪ ተዘጋጅተዋል።

- የትራፊክ ምልክቶች ተከላ ማከናወን እና ማህበራትን ማደራጀት ዋንኛ ስራ ነበር። በ8 ክ/ከተሞች 123 ማህበራትን የማደራጀት ስራ የተሰራ ሲሆን አገልግሎቱም በኮድ 1 ታርጋ ብቻ ይሰጣል።

- የተሳፋሪ መጠን አሽከርካሪውን ጨምሮ 4 ሰው ብቻ ሴሆን የስራ ሰዓት ከጠዋቱ 12 ሰአት እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ብቻ ነው። ህጉን ተላልፈው የተገኙ አሽከርካሪዎች በየደረጃው ቅጣት ይጣልባቸዋል።

- በከተማው መደበኛ ትራንስፖርት በማይገኝበት ከ0 ነጥብ 9 እስከ 2 ነጥብ 45 ኪሎ ሜትር ርቀት ብቻ በ5 ብር ታሪፍ አገልግሎት እንዲሰጡ ተወስኗል።

- የባጃጅ ተሽከርካሪዎች በየትኛውም ርቀት ከ5 ብር በላይ ማስከፈል አይችሉም።

Credit : ADDIS MEDIA NETWORK / FBC

#tikvah

image
Like
Comment
Share
News profile picture
News
5 days ago

#nebe

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤን ያሰናከሉ የህግ አስፈጻሚ አካላት ላይ ፍትሕ ሚኒስቴር ክስ እንዲመሰርት ጠየቀ።

ቦርዱ ይህን የጠየቀው  ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ ጋር በተያያዘ ከሰሞኑ ያጋጠሙ መስተጓጎሎችን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ በሰጠበት ወቅት ነው።

ቦርዱ የፓርቲዎችን ጠቅላላ ጉባኤ ያሰናከሉ የህግ አስፈጻሚ አካላት ላይ ፍትሕ ሚኒስቴር ክስ እንዲመሰርት ከመጠየቅ ባለፈ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ስር የሚተዳደሩ ስብሰባ ቦታዎች እና አዳራሾች ለፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ ክፍት እንዲሆኑም ውሳኔ አሳልፏል።

በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ መሰረት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤያቸውን ቢያንስ በሶስት ዓመት አንድ ጊዜ ማካሄድ አለባቸው።

የፖለቲካ ፓርቲዎች ይህን ግዴታቸውን ለመፈጸም በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ወቅት መስተጓጎል እየገጠማቸው እንደሚገኝ ምርጫ ቦርድ ገልጿል።

ባለፈው እሁድ የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ እንዲሁም ከዛ ቀደም ብሎ የእናት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ መስተጓጎሉ ይታወሳል።

#ኢትዮጵያ_ኢንሳይደር

#tikvahethiopia

imageimage
Like
Comment
Share
News profile picture
News
7 days ago

#attention

• " በድርቅ እና ለረጅም ጊዜ በተከሰተ የፀጥታ ችግር ሴቶች እና ህፃናትን ጨምሮ በርካት ሰዎች ለአደጋ ተጋልጠዋል " - የአማሮ ልዩ ወረዳ

• " ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘ ህፃናትን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ለረሀብ፣ ለበሽታ እና ለሞት እየተዳረጉ ነው " - የቡርጂ ልዩ ወረዳ

በደቡብ ክልል አማሮ እና ቡርጂ ልዩ ወረዳዎች በተከሰተ ድርቅ ምክንያት ከ136 ሺህ በላይ ሰዎች አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ተገልጿል።

#አማሮ

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የአማሮ ልዩ ወረዳን ዋቢ አድርጎ ባሰራጨው መረጃ ፤ በልዩ ወረዳው ለረጅም ጊዜ ዝናብ ባለመጣሉ በ22 ቀበሌዎች ድርቅ ተከስቷል፡፡

በተከሰተው ድርቅ ምክንያት በልዩ ወረዳው ከ96 ሺህ በላይ ሰዎች አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል።

በድርቁ ከ3 ሺህ 500 በላይ የቤት እንስሳት በድርቁ ምክንያት መሞታቸው ተገልጿል።

በልዩ ወረዳው የተከሰቱ የፀጥታ ችግሮች የህብረተሰቡን ተጋላጭነት እንዳባባሱት ልዩ ወረዳው አመልክቷል።

በድርቁ እና ለረጅም ጊዜ በተከሰተው የፀጥታ ችግር ምክንያት ሴቶች እና ህፃናትን ጨምሮ በርካት ሰዎች ለአደጋ መጋለጣቸው ተገልጿል።

የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በተለያየ ጊዜ እርዳታ ቢያደርግም በልዩ ወረዳው ከከተከሰተው ጉዳት አንፃር ድጋፉ በቂ አለመሆኑን ልዩ ወረዳው አሳውቋል።

#ቡርጂ

የቡርጂ ሶያማ ልዩ ወረዳ በበኩሉ በልዩ ወረዳው በተከሰተው ድርቅ 83 ሺህ 528 ዜጎች አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው አሳውቋል።

በልዩ ወረዳው ከ30 ሺህ በላይ እንስሳት መሞታቸውም ተጠቁሟል።

ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘ ህፃናትን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ለረሀብ፣ ለበሽታ እና ለሞት እየተዳረጉ መሆኑ ተገልጿል።

ከክልሉ መንግስት በተጫማሪ የአካባቢው ተወላጆች እና ግለሰቦች እርዳታ ቢያደርጉም በልዩ ወረዳው ከተከሰተው ድርቅ አንፃር የተጎዱ ዜጎችን ለመርዳት በቂ አለመሆኑ ተመላክቷል።

በድርቅ የተጎዱ ዜጎችን ለመርዳት እና መልሶ ለማቋቋም ረጂ ድርጅቶችን ጨምሮ የሚመለከታቸው አካላት ትኩረታቸውን ወደ ልዩ ወረዳው እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

#ኮንሶ

በኮንሶ ዞን በተከሰተ ድርቅ ከ800 ሺህ በላይ ዜጎች ለአስቸኳይ ድጋፍ መዳረጋቸውን ዞኑ አሳውቋል።

ለተከታታይ 5 ዓመት የተከሰተው የዝናብ መዘግየት እና እጥረት ባስከተለው ድርቅ ለአስቸኳይ ድጋፍ የተዳረጉት 822 ሺ 526 ዜጎቻችን ናቸው።
 
የተከሰተው ድርቅ ዜጎች ላይ አስከፊ ጉዳት ከማድረሱ በፊት በችግር ውስጥ ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ ሊደረግ ይገባል ተብሏል።

Credit : #fbc #srta

#tikvahethiopia

imageimage
Like
Comment
Share
News profile picture
News
26 days ago

#ሶማሌላንድ

በሶማሌላንድ ግዛት በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎችና በተቃዋሚ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ ግጭት በርከታ ሰዎች ሰላም ፍለጋ ወደ #ኢትዮጵያ እየገቡ ናቸው።

እስካሁን ግጭት የሸሹ ከ83 ሺ በላይ የሶማሌላንድ ነዋሪዎች ወደ ኢትዮጵያ ድንበር በመዝለቅ በሶማሌ ክልል መስፈራቸው ተነግሯል።

የተመድ የስደተኞች ኮሚሽንን ዋቢ በማድረግ #ሪፖርተር ጋዜጣ እንዳስነበበው "ላስካኑድ" በምትባለው ከተማ በተከሰተው ግጭት፣ የበርካታ የሶማሌላንድ ነዋሪዎችን ሕይወት የተቀጠፈ ሲሆን በርካታ ሴቶችና ሕፃናት ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል፤ ዶሎ ዞን እየገቡ ናቸው።

እንደ ኮሚሽኑ መረጃ ፦

- እስከ  ቅዳሜ የካቲት 11 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ 14 ሺሕ የሚሆኑ አዳዲስ አባወራዎች (ወይም 83 ሺሕ ግለሰብ ስደተኞች) ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል።

- ስደተኞቹ በዶሎ ዞን፤ ቦህ፣ ገልሃሙርና ዳኖድ በተባሉ 3 ወረዳዎች ተጠልለው ይገኛሉ።

- አብዛኞቹ ስደተኞች ባለፈው ሳምንት ነው ወደ ኢትዮጵያ የገቡት።

- ስደተኞች በ3 ወረዳዎች በ13 ቦታዎች ሠፍረው የሚገኙ ሲሆን የተወሰኑት በትምህርት ቤትና መሰል የሕዝብ መገልገያ ሥፍራዎች ላይ ተጠልለዋል፤ ሌሎች ደግሞ ያለ መጠለያ ሜዳ ላይ ይገኛሉ።

- ከሶማሌ ክልል የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ቢሮ ጋር በመሆን ከ1,500 በላይ ለሆኑ በከፍተኛ ሁኔታ ለተጎዱ አባዎራዎች የተለያዩ ቁሳቁሶችና መሰል ድጋፎችን እየተሰጠ ነው።  ለተጨማሪ 9 ሺህ አባዎራዎች በቀጣይ ቀናት ድጋፍ ይደረጋል።

የሶማሌ ክልል፤ የስደተኞችን ወደ ኢትዮጵያ መግባት ያረጋገጠ ሲሆን ከተመድ የስደተኞች ኮሚሽን፣ ከዓለም አቀፍ ፍልሰት ድርጅት፣ እንዲሁም ከኢትዮጵያ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ጋር በመሆን የዳሰሳ ጥናት አካሂዷል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/ER-02-22

imageimage
Like
Comment
Share
News profile picture
News shared a post  
28 days ago

ExpressAfrica profile picture
ExpressAfrica
28 days ago
We're Visible abroad now. Sorry for the inconvenience!

Like
Comment
Load more posts
    Detail
  • Working at ExpressAfrica
  • From Ethiopia
  • Lives in Addis Ababa

  • Male
  • https://expressafrica.et/News
    More info
    My photos 
    1
  • Gifts from
    Following 
    1.2K
  • Kasahun Ts
    devin book
    fans provi
    Dr Manish
    Dr Saurabh
    Hair smith
    sahil posw
    Phuket Div
    全国高等学校サッカー
    Followers 
    33.7K
  • Supriyagup
    animalemal
    chicme dre
    Sehgal Tra
    uffe daphn
    hasenwarde
    ufa betonl
    animalemal
    celebrity
    Likes 
    185
  • Nature
    Tiger Wood
    Small boob
    American s
    brandposit
    iogames
    Friday Nig
    Herbal Rem
    Lifan Bike
    Groups 
    66
  • ፈገግታ ግሩፕ
    We are Afr
    ተነቃቅተናል
    የሳቅ መንደር
    Africa
    ስለኮሮና እናውራ
    ቃና ውስጤ ነው
    አብረን ኖረን አ
    የፍቅር ቃል

© 2023 ExpressAfrica

Language
  • English
  • Amharic
  • Afaan oromoo

  •   FAQs 
  • See COVID-19 Update
  • More
    • Privacy Policy
    • Community Standards
    • About
    • African Wiki
    • Jobs
    • African Places
    • Monetization
    • FAQs
    • COVID-19 (Coronavirus) Updates

Unfriend

Are you sure you want to unfriend?

Report this User

Important!

Are you sure that you want to remove this member from your family?

You have poked News

New member was successfully added to your family list!

Crop your avatar

avatar


Language
  • English
  • Amharic
  • Afaan oromoo
  • Home
  • About
  • Privacy Policy
  • Community Standards
  • Help
  • More
    • African Wiki
    • Jobs
    • African Places
    • Monetization
    • FAQs
    • COVID-19 (Coronavirus) Updates

© 2023 ExpressAfrica

Comment reported successfully.

Post was successfully added to your timeline!

You have reached your limit of friends!

File size error: The file exceeds allowed the limit (6 MB) and can not be uploaded.

Unable to upload a file: This file type is not supported.

We have detected some adult content on the image you uploaded, therefore we have declined your upload process.

Share post on a group

Share to a page

Share to user

Your post was submitted, we will review your content soon.

To upload images, videos, and audio files, you have to upgrade to premium member. Premium Service

Edit Offer

0%

Sell new product

Seller Contact
0%